top of page

የክርስቶስን “ደብረዘይት” “ቢሸፍቱ” በሚል መጠሪያ የለወጡት ጣዖት-አምላኪዎች ለዲያብሎስ አምላካቸው መስዋዕት አበርክተዋል

ደብረ ዘይት = ደብረ ዘይትበሚል ርዕስ ከሦስት ዓመት በፊት ያቀረብኩት ይህ ጽሑፍ፡ በቀድሞዋ ደብረዘይት በሰንበት እለት ለተከሰተው አሳዛኝ እልቂት ትንቢታዊነት ነበረው ማለት ነው...



"ይህችን ብርቱካን እንካ ላጉርስህሲሉ፡ ሾፌራችንም ኧረኧረየርስዎ እጅ ቅቤ ነክቷል፡ ባይሆን የእርሱ ቤንዚንና ዘይት ቢነካውም ቅቤ ከነካው የቤንዚኑ ይሻለኛል፡ እርሱ ያጕርሰኝ!” ብሎ፡ አሳቀን፤ አስገረመን።

መጠሪያ ስሞቻችን፣ የክርስትና ስሞቻችን ወይም ክርስቲያናዊ የሆኑ የቦታ ስሞችን የሚሰጠው መንፈስ ቅዱስ ነው። የእግዚአብሔር አምላክን ገናናነት ለማሳወቅ፡ ለእርሱ ክብር ለመስጠት የምንሰይማቸው ቦታዎች ወይም ከተሞች በርሱ ዘንድ ከፍተኛ ትርጕም አላቸው፤ ለኛም ሰላምን፣ ጽድቅንና በረከትን ያመጡልናል። ሶማሊያዎች እስከ ናዝሬት ከተማ ድረስ ያለው ግዛት የኛ ነው በማለት በህልማቸው የነደፉትን ካርታ ጥገኝነቱን ለሰጣቸው እንግዳ ተቀባይ የአዲስ አበባ ነዋሪ በድፍረት/በንቀት ያሳያሉ። ይህን በቅርብ ሆኜ ለመታዘብ በቅቻለሁ። ለመሆኑ በፊት ጂጂጋ ደርሰው "ናዝሬትዘው ለማለት ያቃታቸው ለምን ይመስለናል? "ናዝሬት" “እየሩሳሌም"፡ የእነዚህ ቦታዎች መጠሪያ ሁልጊዜ የጦርነት ወኔያቸውን ይቀሰቅሰዋል፡ ለምንመልሱን ሁላችንም እናውቀዋለን።

ታዲያ ሁለት ሺህ ዓመታት በሞሉት የክርስትና ታሪካችን፡ ብዛት ያላቸው ምሳሌዎችን ለማየት እየበቃን፡ እንደ "ደብረ ዘይትየመሳሰሉትን የቦታ መጠሪያዎች በዘፈቃድ ለመለወጥ የሚሹ ግለሰቦች በምን ተዓምር አሁን ሊመጡብን ቻሉ? ከተራራው በረሃውን፥ ከቅቤው ቤንዚኑን፥ ከደብረ ዘይት የመኪና ዘይትን የሚመርጥ ትውልድ፡ የመቅሰፍት ምንጭ አይሆንብንምንመቼም ለክርስቶስ ጥላቻ ያላቸው፣ ጸረ-ክርስቶስ የሉሲፈር ፈቃደኛ ወኪሎች ካልሆኑ በቀር እዚህ ድረስ ሊያደርሳቸው የሚችል ሌላ ነገር ሊኖር ይችላልንአይመስለኝምይህ እንደ ቀላል ነገር ተደርጎ መታየት ያለበት ጉዳይ አይደለም፡ ምክኒያቱም በግለሰቦቹ ላይ ሊመጣባቸው የሚችለው ፍርድ ልክ መንፈስ ቅዱስን የሚያስቀይሙት ግለሰቦች ከሚመጣባቸው ኃይለኛ ፍርድ የሚለይ አይሆንምና፤ የመንፈስ ቅዱስን ክብር ደፍረዋልና!

ደብረ ዘይት

ደብረ ዘይት በግእዝ ልሣን ደብረዘይት ማለት የወይራ ተራራ ማለት ነው። ቦታው ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ የሚገኝ የወይራ ዛፍ የበዛበት ተራራ ሲሆን ስሙም ከወይራ ዛፉ:-ደብረ ዘይት (የወይራ ዛፍ ተራራበመሰኘት ተገኝቷል። በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ደብረ ዘይት በዓል ሆኖ የሚከበርበት ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረዘይት ተራራ ላይ ሳለ ለቅዱሳን ደቀመዛሙርቱ ስለ ዓለም ፍጻሜ እና ስለ ዳግም ምጽአቱ ስላስተማራቸዉ በጌታችን ትምህርት መሰረት ነገረ ምጽአቱን (የመምጣቱን ነገርእንድናስታዉስ ወይም እያሰብን እንድንዘጋጅ ለማድረግ ነዉ።

በዚያ ልማድ መሠረት ጌታችን ዓለምን ለማሳለፍ ደግሞ የሚመጣበትን ምልክትና ጠቋሚ ነገር ምን ምን እንደሆነ፣ እርሱ ከመምጣቱ በፊት በዓለም ላይ ምን፥ ምን እንደሚደረግና ምን እንደሚታይ ለደቀመዛሙርቱ የነገራቸው በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ ነው። (ማቴ. 241-51) ስለ ዓለም ሁሉ ቤዛ ለመሆን በሚሰቀልበት ቀን ዋዜማ ማለት በትልቁ ሐሙስ (ጸሎተ ሐሙስበለበሰው ሥጋ የጸለየው ከደብረ ዘይት ጋር ተያይዞ በሚገኘው ቦታ በጌተሴማኒ ነበር። (ማቴ. 2636) በኃላ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላም ለደቀመዛሙርቱ እንዲነግሩ ሲልካቸው፥ “ሂዱና ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል፥ በዚያም ታዩኛላችሁ ብላችሁ ንገሩአቸው፥” ብሎ የላካቸው በደብረ ዘይት ገሊላ ተብላ ትጠራ ወደ ነበረችው ቦታ ነው። (ማቴ. 289) ገሊላውያን ወደ ኤየሩሳሌም ሲመጡ በደብረ ዘይት ያርፍ ነበርና እነሱ ሲያርፉባት የነበረችው ቦታ ገሊላ እየተባለች ትጠራ ነበር። መድኃኔዓለም ክርስቶስ የድኅነት ሥራ ፈጽሞ ወደ ሰማይ ያረገው ከዚህ ተራራ ተነሥቶ ነው። (ሐዋ. 112) ቀደም ብሎም የሆሳእናው የመድኃኔዓለም አስደናቂ ጉዞ የተጀመረው ከደብረ ዘይት ሥር ነበር። (ማቴ. 211-16)

ወስብሓት ለእግዚአብሔር

__

 
 
 

Recent Posts

See All

Comments


bottom of page