top of page

ከኃጢአተኞች ጋር ነፍሴን ፥ ከደም ሰዎችም ጋር ሕይወቴን አታጥፋ


https://youtu.be/pFV88DX2wLM

በእጃቸው ተንኰል አለባቸው፥ ቀኛቸውም መማለጃ ተሞልታለች።

<መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፳፭>መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፳፭>

፩ አቤቱ፥ እኔ በየውሃቴ ሄጃለሁና ፍረድልኝ፤ በእግዚአብሔርም አምኛለሁና አልናወጥም።

፪ አቤቱ፥ ፍተነኝ መርምረኝም፤ ኵላሊቴንና ልቤን ፍተን።

፫ ምሕረትህ በዓይኔ ፊት ነውና፥ በእውነትህም ተመላለስሁ።

፬ በከንቱ ሸንጎ አልተቀመጥሁም፥ ከዓመፀኞችም ጋር አልገባሁም።

፭ የክፉዎችን ማኅበር ጠላሁ፥ ከዝንጉዎችም ጋር አልቀመጥም።

፮ እጆቼን በንጽሕና አጥባለሁ፤ አቤቱ፥ መሠዊያህን እዞራለሁ፥

፯ የምስጋናን ድምፅ እሰማ ዘንድ፥ ተአምራትህንም ሁሉ እነግር ዘንድ።

፰ አቤቱ፥ የቤትህን ስፍራ የክብርህንም ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።

፱ ከኃጢአተኞች ጋር ነፍሴን፥ ከደም ሰዎችም ጋር ሕይወቴን አታጥፋ።

፲ በእጃቸው ተንኰል አለባቸው፥ ቀኛቸውም መማለጃ ተሞልታለች።

፲፩ እኔ ግን በየውሃቴ ሄጃለሁ፤ አድነኝ ማረኝም።

፲፪ እግሮቼ በቅንነት ቆመዋልና፤ አቤቱ፥ በማኅበር አመሰግንሃለሁ።

______________________________

Comments


bottom of page